Posts

ነገ ላይ እንድትደርስ የትናንቱን አትርሳ

Image
✍ ምክርን ብትሰማ በነጻ ትማራለህ። ምክርን አልሰማ ብትል ግን በዋጋ እንደምትማር እወቀው። በዋጋ መማር ግን አድካሚ ደግሞም የሚያስመርር ነው። ብልህ ከሆንህ በሰው ከደረሰበት ትማራለህ፣ ሞኝ ከሆንህ ግን በራስህ ሲደርስ ትማራለህ። ✍ የታየህን አሳይ፣ ያልታየህን አጥራው። በደንብ ያልተረዳኸውን አታስተምረው። ያልቀመስከውን ለሰው አትጋብዝ። የሰማኸውን ሁሉ አትመን። ያየኸውን ሁሉ ስጡኝ፣ የተናገርከውን ሁሉ ፈፅሙ አትበል። የሰጠኽውን እርሳ እንጂ አታውራ። ፍፃሜውን ሳታይ ምስጋና አታብዛ። ቀኑ ሳይመሽ ቀኑ ጥሩ ነው አትበል። ✍ ዓይንህ የፊቱን ቢያይ ልብህ የኋላውን ያስብ። ነገ ላይ እንድትደርስ የትናንቱን አትርሳ። የምትሄድበት እናዳይጠፋህ የመጣህበትን አትዘንጋ፡፡  ምክረ አበው

ፈጣሪ ሆይ አትማረኝ!

Image
በአንድ ወቅት አንዲት ሴት ጫካ ውስጥ ብቻዋን የምትኖር ወጣት ነበረች። ሁልጊዜ ጥዋት ጥዋት እየተነሳች ወደ ባህር ዳርቻ በመሄድ ‹‹ፈጣሪ ሆይ አትማረኝ! አትማረኝ!›› እያለች ትፀልያለች። ታድያ ከባህሩ መሀል ላይ ካለች ደሴት ላይ የሚኖር አንድ ወጣት ይህችን ልጅ ፀሎት ሁልጊዜ ይሰማና ይገረም ነበር። ‹‹ወይ አለማወቅ›› ብሎም ከራሱም ጋር ያወራ ነበር። እና አንድ ቀን ይህች ሴት እንደተለመደው ወደ ባህሩ ዳርቻ ሄዳ ስትፀልይ ያያት ያ ወጣት በትንሽ ታንኳ(ጀልባ) ተሳፍሮ ወደ ባህሩ ዳርቻ ይሄድና ‹‹አንቺ ሴት ሁልጊዜ አትማረኝ አትማረኝ እያልሽ ስትፀልይ እሰማለሁ ይህ ደግሞ ትክክል አይደለም አላዋቂነት ነው። ስለዚህ ከዛሬ ጀምሮ ‹ማረኝ ማረኝ ማረኝ› እያልሽ ነው መፀለይ ያለብሽ›› ብሏት በመጣበት አቅጣጫ ተመለሰ። ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ይህች ሴት ‹‹ቆይ ይህ ወጣት ምን ብለሽ ነበር ፀልይ ያለኝ… እረሳሁት›› ብላ በባህሩ ላይ እየሮጠች ጀልባዋ ጋር ከደረሰች በኋላ ‹‹ወንድም ሆይ የነገርከኝን ረሳሁት፤ ምን ብለሽ ነበር ፀልይ ያልከኝ?›› ስትል ጠየቀችው? ይህ ወጣትም በባህሩ ላይ መሮጥ መቻሏን አይቶ በጣም በመደነቅ እና በመደመም ‹‹በይ እህቴ ቀድሞ ስትፀልይ እንደነበረው ፀልይ›› አላት ይባላል። ምን ለማለት ፈልጌ ነው አንተ ትክክል ነው ብለህ ያመንክበትን ነገር ያለምንም ማፈር ወይም መሸማቀቅ አድርገው ወይም ተግብረው። ሌሎች ሰዎች በእነሱ አተያይና አመለካከት ሊቃኙህ ቢሞክሩ ፍፁም እንዳትሰማቸው። ትክክል ነኝ ብለህ ካመንክበት በቃ አድርገው።

ሳያስቡ ከመኖር እያሰቡ መሞት ይሻላል

Image
እጅግ አስቀያሚ መልክ ያለው፣ ትልቅ መላጣ ራስ፣ ትንሽ ፊት፣ ረጅም ቅጥ ያጣ ፂም፣ ጨቅጫቃ ሚስት የነበረው እና ሲበዛ ተከራካሪ እና ተጫዋች ነው።  ገና በጠዋቱ ማልዶ ተነስቶ ቁርሱን በልቶ፣ አሮጌ ልብስ ለብሶ በባዶ እግሩ ወደ ከተማ ሄዶ ህዝብ በተሰበሰበበት ስፍራ አስገራሚውን አዲስ ሃሳብ አካፈፍሎ ማታ ላይ ከገበያተኛው ጋር ባዶ እጁን ወደ ቤቱ ይመለስ ነበር። ግሪክ የእውቀት አማልዕክት መናፍስት  የመረቋት፣ ሃሳብ የተፀነሰባት እና የተወለደባት ብቻ ሳትሆን ሃሳብ የተከበረባት ውብ ሃገር ነች። ከዛሬ 2500 ዓመት በፊት ስልጡን ህዝብ የሚኖርባት ለአዲስ አስተሳሰብ ትልቅ ዋጋ (credit) ሰጥታ ሃሳብ የሚወለድባቸው አደባባዮች የገነባች የጠቢባን ምድር ግሪክን አለማድነቅ ምቀኝነት ነው። ህዝቡስ ቢሆን ፍቅር ነው.... አዲስ ሃሳብ ለመስማት ስራየ ብሎ አደባባዮችን ያጨናንቅ ነበር። ማንም አዲስ ሃሳብ ያለው ሰው ወጥቶ ሃሳቡን በነጻነት ይናገር ነበር። የእኛ ህዝብ አዲስ ሃሳብ መስማትም ማመንጨትም አይወድም.... ትልቁ የሃገሪቱ ራስ ምታት ይኸው ነው። አሪዮስ ፋጎስ በሚባለው መድረካቸው የጠቢባን ጥበብ እንደጉድ ይፈሳል። ቅዱስ ጳውሎስም አዲስ ሃሳብ አለኝ ብሎ በመውጣት በሚገባ ኢየሱስን ሰብኮላቸዋል። ከሶቅራጥስ በፊት ከቴለስ እስከ ሄራክሊተስ ድረስ ስለ ዓለማት ዓፈጣጠር cosmology ይጠይቁ ይመራመሩ ነበር። ሶቅራጥስ መጣና ስለ ህዋ(space) ማጥናት ብዙም አያዋጣም ሁሉም እውቀት፣ እውነት እና ጥበብ ያለችው ከሰው ውስጥ ነው አለ። ይተነትነው ገባ.... የግሪክን ወጣቶች ቀልብ ያለ ምንም ጠቅልሎ ማረከ፣ ቆነጃጅት በሶቅራጥስ ጥበብ መነኮሱ፣ አማልክቶች ሁሉ ለሶቅራጥስ ሃሳብ እጅ ሰጡ.... ዓለምን ከብርቱ ድባቴ ቀሰቀሳት፣ አዛወንቶች...

ማንም የሌለውን ነው የሚወስደው

Image
 ኔልሰን ማንዴላ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የህግ ትምህርት  በሚማሩበት ጊዜ ነጭ ፕሮፌሰር አስተማሪ ነበራቸው። ስሙም ፒተር ይባላል፡፡ አንድ ቀን ፕሮፌሰር ፒተር በአንድ ምግብ ቤት ምግባቸውን እየበሉ ሳለ ማንዴላ በአጋጣሚ ምግብ ይዘው ከአጠገባቸው ይቀመጣሉ። ፒተርም "አቶ ማንዴላ! አሳማና 'ርግብ ለመብል አብረው አይቀመጡም!" ሲላቸው ብልሁ ማንዴላም "አይጨነቁ ፕሮፌሰር በርሬ እሄዳለሁ" ብለዋቸው ሌላ ወንበር ላይ ይቀመጣሉ። በዚህ የተናደደው ፒተር በሌላ ቀን ቂሙን ሊወጣበት ያስባል። አንድ ቀንም ፕሮፌሰሩ ክላስ ውስጥ እያስተማሩ፡- "ማንዴላ በመንገድ ላይ እየሄድክ ሁለት ቦርሳዎችን ብታገኝና በአንደኛው ቦርሳ ገንዘብ' በሌላኛው ቦርሳ ደግሞ 'ጥበብ' ቢኖር የትኛውን ትወስዳለህ?" ብሎ ማንዴላን ሲጠይቀው ማንዴላም "ገንዘቡን እወስደዋለሁ" ብሎ መለሰለት። ፕሮፌሰሩም በድል አድራጊነት "አንተ ሞኝ ነህ፣ እኔ አንተን ብሆን ኖሮ ጥበብ ያለበትን ቦርሳ እወስድ ነበር" ሲለው ማንዴላ ፈገግ እያለ "ልክ ነህ ማንም የሌለውን ነው የሚወስደው" አለው። በዚህ ሁሉ ነገር የተበሳጨው ፕሮፌሰር ፒተር የማንዴላ የፈተና ወረቀት ላይ 'ደደብ' ብሎ ይፅፋል። ሌሎች ተማሪዎች የታረመላቸውን የፈተና ወረቀት ሲያዩ ማንዴላ ደደብ የሚለውን ፅሁፍ ከወረቀቱ ላይ አየና ተገረመ፡፡ ከዛም ወደ ፕሮፌሰሩ ሄዶ "ይቅርታ ቲቸር ፊርማህን ብቻ ነው ያስቀመጥክልኝ ውጤቴን ረስተኸዋል" ብሎት እርፍ፡፡

አስደናቂ ሴቶችና አስደናቂ ተፈጥሮ ያላት ሀገሀር

Image
የሴቶቿ ቁጥር ከወንዶች በመብለጡ ምክንያት ሴቶቿ ፍቅረኛና ባል ፍለጋ ስለሚንከራተቱባት፣ በአውሮፓ ውስጥ እጅግ ፈጣን የሆኑ የኢንተርኔት አገልግሎት ስላላት ሽቅርቅር ምድር፣ ቢራ እንደ ውሃ በሚጠጣባትና በቢራ ፋብሪካዎች ስለተጨናነቀችው ግዛት፣ ተፈጥሮና ዘመናዊነትን አስማምታ የጎብኝዎችን ልብ ከፍ ዝቅ ስለምታደርገው አንዲት ሃገር እናወራለን፣ ከማውራትም አልፈን ዙሪያ ገባዋን አብረን እንጎበኛለን። https://youtu.be/18-RmF6uGqc የጥንታዊ ደኖች እና የዘመናዊ ከተሞች ቅይጥ ምድር ወደሆነችው፣ የስነ-ህዝብ ለውጥ ለሚስትና ፍቅረኛ ፈላጊ ወንዶች ገነትን ለፈጠረባት፣ ማራኪ መልክ፣ ለግላጋ ቁመት ፣ ሰማያዊ አይኖች፣ ከፍ ያለ ጉንጭ፣ የስላቭ እና የኖርዲክ ጂኖች ውህድ ባህሪ ያላቸው ቆነጃጅቶች የሚኖሩባት በአጠቃላይ ጭንቅላት የሚያዞር ውበት ጥምር ውበት ምድር እንኳን ወደ ላቲቪያ፣ ባልቲክ ግዛት በደህና መጡ፤ @@@@@ አብረውን ወደዚች ሀገር ከተጓዙ ወደው ብቻ ሳይሆን ተገደውም በቆነጃጅት ሴቶች ከንፈርዎን ቢሳሙ ወይም ድንገተኛ የአንሶላ እንጋፈፍ ግብዣ ቢቀርብልዎ፣ ወይም ደግሞ የእንጋባና አለማችንን እየቀጨን አብረን እንኑር ጥያቄ ቢቀርብልዎ ውሳኔው የእርስዎ ነው። ለምን ካሉን መልሱ ወዲህ ነው፣ ላቲቪያ የሴቶች ቁጥር ከወንዶቹ ዜጎቿ በመብለጡ ምክንያት ቆነጃጅት ሴቶቿ ፍቅረኛና በባል እጥረት እንዲሁም በወሲብ ጥም የሚሰቃዩ በመሆናቸው በተለይ የሌላ አገር ዜጎችን በፍቅር ለማጥመድ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፣ የቆነጃጅቶችን ነገር በኃላ ላይ ዘርዝረን እንመለከተው ዘንድ እናቆየውና ላቲቪያን በወፍ በረር እንጎበኛት ዘንድ ወደናል፣ አብረን እንጓዝ።  በሰሜን አውሮፓ የባልቲክ ክልል ውስጥ የምትገኘው ላቲቪያ፣ ትንሽ ሀገር ብትሆንም ትልቅ ልብ አላት። ይህ...

ብልሁ ሰዓሊ

Image
ብልሁ ሰዓሊ አንድ ዓይና የሆነ አንድ አምባገነን ሱልጣን ሦስት ሰዓሊያንን ጠርቶ የእሱን ምስል በስዕል ቀርጸው እንዲያስቀምጡለት ካሳሰባቸው በኋላ አያይዞም መጥፎ እይታ ያለው አድርጎ የሳለኝን እቀጣለሁ፡፡ በጥሩ ሁኔታ የሳለውን ደግሞ እሸልማለሁ ሲል አስጠነቀቃቸው፡፡ የመጀመሪያው ሰዓሊ ሱልጣኑ አንድ ዓይና መሆኑን አጋልጦ የሚያሳይ ስዕል አድርጎ ሳለው፡፡ የሱልጣንነቱን ክብር የሚነካ በመሆኑ ቅጣት ተላለፈበት፡፡ ሁለተኛው ሰዓሊ ደግሞ ሱልጣኑ ሁለት ዓይን እንዳለው አስመስሎ ሳለው፡፡ ይኸ ሰዓሊም ሱልጣኑን የማታለል ስራ ስለሆነ የሠራው ቅጣቱን ተቀበለ፡፡ ሶስተኛው ሰዓሊ ግን የጎንዮሽ እይታ እንዲሰጥና ደናውን ዓይኑን አጉልቶ በሚያሳይ ሁኔታ ሳለው፡፡ በዚህም ሱልጣኑ ተደስቶ የወርቅና የክብር ሽልማቱን አበረከተለት፡፡  ‹‹››‹‹›› አንዳንድ ጊዜ እውነትን እውነት ማለት በቂ ላይሆን ይችላል፡፡ ወይም በሌላ አባባል እውነት እራቁቷን ስትቀርብ የሚቀበላት ትንሽ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ደረቅ እውነታ ካልተዋዛ ለመዋጥ ያስቸግራል፡፡ እውነትነቱ ባይቀየርም፡፡ እውነትን ለመመስከር እውነት ሰሚ ጀሮ ያስፈልጋል፡፡ እውነትን አድማጭ በሌለበት ባዶ ሜዳ ላይ መለፍለፍ ደግሞ ከእውነት ጋር አዘቅት መግባትና ዋጋ-ቢስ መሆን ነው፡፡ በዋጋ-ቢስ እውነትና በሐሰት መካከል ያለው ልዩነት ደግሞ ርቀቱ የጋት ያህል ነው ይላሉ እውቁ የንግድ ሰው ወልደሔር ይዘንጋው በግለ ታሪክ መጽሐፋቸው፡፡

ገረዲቱ - ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት

Image
ገረዲቱ እያንዳንዱ ቀን የራሱ የሆነ በጎም ሆነ ደግ ታሪክ ሳይስተናገድበት አያልፍም፤ በሥነ ፍጥረት ታሪክ ውስጥ ብትመለከቱ ምንም ሳይሠራ ያለፈ ሰው ታገኙ ይሆናል እንጅ ምንም ሥራ ያልተሠራበት ቀን አታገኙም፤ ምክንያቱም ጊዜ የተፈጠረው ለሥራ ነውና:: ከመጀመሪያዋ ጊዜ ጀምሮ እግዚአብሔር ያላ ሥራ ያሳለፋት ጊዜ አትገኝም፡፡ በእያንዳንዳችንም ሕወት ውስጥ እለታት የየራሳቸው የሆነ ልዩ ልዩ ታሪክ አላቸው፡፡ አንዳንዶቹ የወደቅንባቸው አንዳንዶቹ የተነሣንባቸው፣ የተደሰትንባቸውና ያለቀስንባቸው፣ እግዚአብሔርን  ያገኘንባቸው ወይም ከሰይጣን ጋር ማኅበርተኛ የሆንባቸው ሊሆኑ ይችላሉ፡፡  ለዛሬው እንኳን ይህን የምላችሁ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሰፊ ታሪክ ስለተመዘገበለት አንድ ቅዱስ ሰው ልነግራችሁ ፈልጌ ነው፤ ሰውየው ገሊላዊ፣ ትውልዱና ነገዱ ዕብራዊ ሲሆን ያደገው በታላቁ የገሊላ ባሕር አጠገብ ነው ዋና ሥራው አሣ አጥማጅነት ሲሆን የቀደመ ስሙ ስምዖን ወልደ ዮና የክርስትና ስሙ ደግሞ ጴጥሮስ ይባላል፡፡ ይህ ሰው እግዚአብሔር በእርጅና ዘመኑ የባረከው ሰው ነው፤ መቸም እግዚአብሔር ለእያንዳንደችን ያዘጋጃት የመጎብኘት ቀን እንዳለች እናምናለን፣ ከዚህም የተነሣ አንዳንዶችን  በማሕጸን ሳሉ እንደነ ኤርምያስና ዮሐንስ መጥምቅ ያሉትን፣አንዳንዶችን በጨቅላነት እድሜ እንደነ ቅዱስ ቂርቆስ፣ አንዳንዶችን በወጣትነት እንደነ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊና እንደነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያሉትን አንዳንዶችን በእርጅና ዘመናቸው እንደነ ቅዱስ ጴጥሮስ ያሉትን ጎብኝቷቸዋል ፡፡ ከሰው የሚጠበቅ የሚጎበኝበትን ቀን ደጅ መጥናት ነው እንጅ ሌላው የእግዚአብሔር ድርሻ ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም እግዚአብሔር የወሰነለት ቀን ስትደርስ በትጋት ሆኖ ከሚሠራበት ቦታ ሂዶ ጎበኘው፣ ለ...