Posts

ነገ ላይ እንድትደርስ የትናንቱን አትርሳ

Image
✍ ምክርን ብትሰማ በነጻ ትማራለህ። ምክርን አልሰማ ብትል ግን በዋጋ እንደምትማር እወቀው። በዋጋ መማር ግን አድካሚ ደግሞም የሚያስመርር ነው። ብልህ ከሆንህ በሰው ከደረሰበት ትማራለህ፣ ሞኝ ከሆንህ ግን በራስህ ሲደርስ ትማራለህ። ✍ የታየህን አሳይ፣ ያልታየህን አጥራው። በደንብ ያልተረዳኸውን አታስተምረው። ያልቀመስከውን ለሰው አትጋብዝ። የሰማኸውን ሁሉ አትመን። ያየኸውን ሁሉ ስጡኝ፣ የተናገርከውን ሁሉ ፈፅሙ አትበል። የሰጠኽውን እርሳ እንጂ አታውራ። ፍፃሜውን ሳታይ ምስጋና አታብዛ። ቀኑ ሳይመሽ ቀኑ ጥሩ ነው አትበል። ✍ ዓይንህ የፊቱን ቢያይ ልብህ የኋላውን ያስብ። ነገ ላይ እንድትደርስ የትናንቱን አትርሳ። የምትሄድበት እናዳይጠፋህ የመጣህበትን አትዘንጋ፡፡  ምክረ አበው

ፈጣሪ ሆይ አትማረኝ!

Image
በአንድ ወቅት አንዲት ሴት ጫካ ውስጥ ብቻዋን የምትኖር ወጣት ነበረች። ሁልጊዜ ጥዋት ጥዋት እየተነሳች ወደ ባህር ዳርቻ በመሄድ ‹‹ፈጣሪ ሆይ አትማረኝ! አትማረኝ!›› እያለች ትፀልያለች። ታድያ ከባህሩ መሀል ላይ ካለች ደሴት ላይ የሚኖር አንድ ወጣት ይህችን ልጅ ፀሎት ሁልጊዜ ይሰማና ይገረም ነበር። ‹‹ወይ አለማወቅ›› ብሎም ከራሱም ጋር ያወራ ነበር። እና አንድ ቀን ይህች ሴት እንደተለመደው ወደ ባህሩ ዳርቻ ሄዳ ስትፀልይ ያያት ያ ወጣት በትንሽ ታንኳ(ጀልባ) ተሳፍሮ ወደ ባህሩ ዳርቻ ይሄድና ‹‹አንቺ ሴት ሁልጊዜ አትማረኝ አትማረኝ እያልሽ ስትፀልይ እሰማለሁ ይህ ደግሞ ትክክል አይደለም አላዋቂነት ነው። ስለዚህ ከዛሬ ጀምሮ ‹ማረኝ ማረኝ ማረኝ› እያልሽ ነው መፀለይ ያለብሽ›› ብሏት በመጣበት አቅጣጫ ተመለሰ። ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ይህች ሴት ‹‹ቆይ ይህ ወጣት ምን ብለሽ ነበር ፀልይ ያለኝ… እረሳሁት›› ብላ በባህሩ ላይ እየሮጠች ጀልባዋ ጋር ከደረሰች በኋላ ‹‹ወንድም ሆይ የነገርከኝን ረሳሁት፤ ምን ብለሽ ነበር ፀልይ ያልከኝ?›› ስትል ጠየቀችው? ይህ ወጣትም በባህሩ ላይ መሮጥ መቻሏን አይቶ በጣም በመደነቅ እና በመደመም ‹‹በይ እህቴ ቀድሞ ስትፀልይ እንደነበረው ፀልይ›› አላት ይባላል። ምን ለማለት ፈልጌ ነው አንተ ትክክል ነው ብለህ ያመንክበትን ነገር ያለምንም ማፈር ወይም መሸማቀቅ አድርገው ወይም ተግብረው። ሌሎች ሰዎች በእነሱ አተያይና አመለካከት ሊቃኙህ ቢሞክሩ ፍፁም እንዳትሰማቸው። ትክክል ነኝ ብለህ ካመንክበት በቃ አድርገው።

ሳያስቡ ከመኖር እያሰቡ መሞት ይሻላል

Image
እጅግ አስቀያሚ መልክ ያለው፣ ትልቅ መላጣ ራስ፣ ትንሽ ፊት፣ ረጅም ቅጥ ያጣ ፂም፣ ጨቅጫቃ ሚስት የነበረው እና ሲበዛ ተከራካሪ እና ተጫዋች ነው።  ገና በጠዋቱ ማልዶ ተነስቶ ቁርሱን በልቶ፣ አሮጌ ልብስ ለብሶ በባዶ እግሩ ወደ ከተማ ሄዶ ህዝብ በተሰበሰበበት ስፍራ አስገራሚውን አዲስ ሃሳብ አካፈፍሎ ማታ ላይ ከገበያተኛው ጋር ባዶ እጁን ወደ ቤቱ ይመለስ ነበር። ግሪክ የእውቀት አማልዕክት መናፍስት  የመረቋት፣ ሃሳብ የተፀነሰባት እና የተወለደባት ብቻ ሳትሆን ሃሳብ የተከበረባት ውብ ሃገር ነች። ከዛሬ 2500 ዓመት በፊት ስልጡን ህዝብ የሚኖርባት ለአዲስ አስተሳሰብ ትልቅ ዋጋ (credit) ሰጥታ ሃሳብ የሚወለድባቸው አደባባዮች የገነባች የጠቢባን ምድር ግሪክን አለማድነቅ ምቀኝነት ነው። ህዝቡስ ቢሆን ፍቅር ነው.... አዲስ ሃሳብ ለመስማት ስራየ ብሎ አደባባዮችን ያጨናንቅ ነበር። ማንም አዲስ ሃሳብ ያለው ሰው ወጥቶ ሃሳቡን በነጻነት ይናገር ነበር። የእኛ ህዝብ አዲስ ሃሳብ መስማትም ማመንጨትም አይወድም.... ትልቁ የሃገሪቱ ራስ ምታት ይኸው ነው። አሪዮስ ፋጎስ በሚባለው መድረካቸው የጠቢባን ጥበብ እንደጉድ ይፈሳል። ቅዱስ ጳውሎስም አዲስ ሃሳብ አለኝ ብሎ በመውጣት በሚገባ ኢየሱስን ሰብኮላቸዋል። ከሶቅራጥስ በፊት ከቴለስ እስከ ሄራክሊተስ ድረስ ስለ ዓለማት ዓፈጣጠር cosmology ይጠይቁ ይመራመሩ ነበር። ሶቅራጥስ መጣና ስለ ህዋ(space) ማጥናት ብዙም አያዋጣም ሁሉም እውቀት፣ እውነት እና ጥበብ ያለችው ከሰው ውስጥ ነው አለ። ይተነትነው ገባ.... የግሪክን ወጣቶች ቀልብ ያለ ምንም ጠቅልሎ ማረከ፣ ቆነጃጅት በሶቅራጥስ ጥበብ መነኮሱ፣ አማልክቶች ሁሉ ለሶቅራጥስ ሃሳብ እጅ ሰጡ.... ዓለምን ከብርቱ ድባቴ ቀሰቀሳት፣ አዛወንቶች...

ማንም የሌለውን ነው የሚወስደው

Image
 ኔልሰን ማንዴላ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ የህግ ትምህርት  በሚማሩበት ጊዜ ነጭ ፕሮፌሰር አስተማሪ ነበራቸው። ስሙም ፒተር ይባላል፡፡ አንድ ቀን ፕሮፌሰር ፒተር በአንድ ምግብ ቤት ምግባቸውን እየበሉ ሳለ ማንዴላ በአጋጣሚ ምግብ ይዘው ከአጠገባቸው ይቀመጣሉ። ፒተርም "አቶ ማንዴላ! አሳማና 'ርግብ ለመብል አብረው አይቀመጡም!" ሲላቸው ብልሁ ማንዴላም "አይጨነቁ ፕሮፌሰር በርሬ እሄዳለሁ" ብለዋቸው ሌላ ወንበር ላይ ይቀመጣሉ። በዚህ የተናደደው ፒተር በሌላ ቀን ቂሙን ሊወጣበት ያስባል። አንድ ቀንም ፕሮፌሰሩ ክላስ ውስጥ እያስተማሩ፡- "ማንዴላ በመንገድ ላይ እየሄድክ ሁለት ቦርሳዎችን ብታገኝና በአንደኛው ቦርሳ ገንዘብ' በሌላኛው ቦርሳ ደግሞ 'ጥበብ' ቢኖር የትኛውን ትወስዳለህ?" ብሎ ማንዴላን ሲጠይቀው ማንዴላም "ገንዘቡን እወስደዋለሁ" ብሎ መለሰለት። ፕሮፌሰሩም በድል አድራጊነት "አንተ ሞኝ ነህ፣ እኔ አንተን ብሆን ኖሮ ጥበብ ያለበትን ቦርሳ እወስድ ነበር" ሲለው ማንዴላ ፈገግ እያለ "ልክ ነህ ማንም የሌለውን ነው የሚወስደው" አለው። በዚህ ሁሉ ነገር የተበሳጨው ፕሮፌሰር ፒተር የማንዴላ የፈተና ወረቀት ላይ 'ደደብ' ብሎ ይፅፋል። ሌሎች ተማሪዎች የታረመላቸውን የፈተና ወረቀት ሲያዩ ማንዴላ ደደብ የሚለውን ፅሁፍ ከወረቀቱ ላይ አየና ተገረመ፡፡ ከዛም ወደ ፕሮፌሰሩ ሄዶ "ይቅርታ ቲቸር ፊርማህን ብቻ ነው ያስቀመጥክልኝ ውጤቴን ረስተኸዋል" ብሎት እርፍ፡፡

አስደናቂ ሴቶችና አስደናቂ ተፈጥሮ ያላት ሀገሀር

Image
የሴቶቿ ቁጥር ከወንዶች በመብለጡ ምክንያት ሴቶቿ ፍቅረኛና ባል ፍለጋ ስለሚንከራተቱባት፣ በአውሮፓ ውስጥ እጅግ ፈጣን የሆኑ የኢንተርኔት አገልግሎት ስላላት ሽቅርቅር ምድር፣ ቢራ እንደ ውሃ በሚጠጣባትና በቢራ ፋብሪካዎች ስለተጨናነቀችው ግዛት፣ ተፈጥሮና ዘመናዊነትን አስማምታ የጎብኝዎችን ልብ ከፍ ዝቅ ስለምታደርገው አንዲት ሃገር እናወራለን፣ ከማውራትም አልፈን ዙሪያ ገባዋን አብረን እንጎበኛለን። https://youtu.be/18-RmF6uGqc የጥንታዊ ደኖች እና የዘመናዊ ከተሞች ቅይጥ ምድር ወደሆነችው፣ የስነ-ህዝብ ለውጥ ለሚስትና ፍቅረኛ ፈላጊ ወንዶች ገነትን ለፈጠረባት፣ ማራኪ መልክ፣ ለግላጋ ቁመት ፣ ሰማያዊ አይኖች፣ ከፍ ያለ ጉንጭ፣ የስላቭ እና የኖርዲክ ጂኖች ውህድ ባህሪ ያላቸው ቆነጃጅቶች የሚኖሩባት በአጠቃላይ ጭንቅላት የሚያዞር ውበት ጥምር ውበት ምድር እንኳን ወደ ላቲቪያ፣ ባልቲክ ግዛት በደህና መጡ፤ @@@@@ አብረውን ወደዚች ሀገር ከተጓዙ ወደው ብቻ ሳይሆን ተገደውም በቆነጃጅት ሴቶች ከንፈርዎን ቢሳሙ ወይም ድንገተኛ የአንሶላ እንጋፈፍ ግብዣ ቢቀርብልዎ፣ ወይም ደግሞ የእንጋባና አለማችንን እየቀጨን አብረን እንኑር ጥያቄ ቢቀርብልዎ ውሳኔው የእርስዎ ነው። ለምን ካሉን መልሱ ወዲህ ነው፣ ላቲቪያ የሴቶች ቁጥር ከወንዶቹ ዜጎቿ በመብለጡ ምክንያት ቆነጃጅት ሴቶቿ ፍቅረኛና በባል እጥረት እንዲሁም በወሲብ ጥም የሚሰቃዩ በመሆናቸው በተለይ የሌላ አገር ዜጎችን በፍቅር ለማጥመድ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፣ የቆነጃጅቶችን ነገር በኃላ ላይ ዘርዝረን እንመለከተው ዘንድ እናቆየውና ላቲቪያን በወፍ በረር እንጎበኛት ዘንድ ወደናል፣ አብረን እንጓዝ።  በሰሜን አውሮፓ የባልቲክ ክልል ውስጥ የምትገኘው ላቲቪያ፣ ትንሽ ሀገር ብትሆንም ትልቅ ልብ አላት። ይህ...

ብልሁ ሰዓሊ

Image
ብልሁ ሰዓሊ አንድ ዓይና የሆነ አንድ አምባገነን ሱልጣን ሦስት ሰዓሊያንን ጠርቶ የእሱን ምስል በስዕል ቀርጸው እንዲያስቀምጡለት ካሳሰባቸው በኋላ አያይዞም መጥፎ እይታ ያለው አድርጎ የሳለኝን እቀጣለሁ፡፡ በጥሩ ሁኔታ የሳለውን ደግሞ እሸልማለሁ ሲል አስጠነቀቃቸው፡፡ የመጀመሪያው ሰዓሊ ሱልጣኑ አንድ ዓይና መሆኑን አጋልጦ የሚያሳይ ስዕል አድርጎ ሳለው፡፡ የሱልጣንነቱን ክብር የሚነካ በመሆኑ ቅጣት ተላለፈበት፡፡ ሁለተኛው ሰዓሊ ደግሞ ሱልጣኑ ሁለት ዓይን እንዳለው አስመስሎ ሳለው፡፡ ይኸ ሰዓሊም ሱልጣኑን የማታለል ስራ ስለሆነ የሠራው ቅጣቱን ተቀበለ፡፡ ሶስተኛው ሰዓሊ ግን የጎንዮሽ እይታ እንዲሰጥና ደናውን ዓይኑን አጉልቶ በሚያሳይ ሁኔታ ሳለው፡፡ በዚህም ሱልጣኑ ተደስቶ የወርቅና የክብር ሽልማቱን አበረከተለት፡፡  ‹‹››‹‹›› አንዳንድ ጊዜ እውነትን እውነት ማለት በቂ ላይሆን ይችላል፡፡ ወይም በሌላ አባባል እውነት እራቁቷን ስትቀርብ የሚቀበላት ትንሽ ይሆናል ማለት ነው፡፡ ደረቅ እውነታ ካልተዋዛ ለመዋጥ ያስቸግራል፡፡ እውነትነቱ ባይቀየርም፡፡ እውነትን ለመመስከር እውነት ሰሚ ጀሮ ያስፈልጋል፡፡ እውነትን አድማጭ በሌለበት ባዶ ሜዳ ላይ መለፍለፍ ደግሞ ከእውነት ጋር አዘቅት መግባትና ዋጋ-ቢስ መሆን ነው፡፡ በዋጋ-ቢስ እውነትና በሐሰት መካከል ያለው ልዩነት ደግሞ ርቀቱ የጋት ያህል ነው ይላሉ እውቁ የንግድ ሰው ወልደሔር ይዘንጋው በግለ ታሪክ መጽሐፋቸው፡፡

ገረዲቱ - ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት

Image
ገረዲቱ እያንዳንዱ ቀን የራሱ የሆነ በጎም ሆነ ደግ ታሪክ ሳይስተናገድበት አያልፍም፤ በሥነ ፍጥረት ታሪክ ውስጥ ብትመለከቱ ምንም ሳይሠራ ያለፈ ሰው ታገኙ ይሆናል እንጅ ምንም ሥራ ያልተሠራበት ቀን አታገኙም፤ ምክንያቱም ጊዜ የተፈጠረው ለሥራ ነውና:: ከመጀመሪያዋ ጊዜ ጀምሮ እግዚአብሔር ያላ ሥራ ያሳለፋት ጊዜ አትገኝም፡፡ በእያንዳንዳችንም ሕወት ውስጥ እለታት የየራሳቸው የሆነ ልዩ ልዩ ታሪክ አላቸው፡፡ አንዳንዶቹ የወደቅንባቸው አንዳንዶቹ የተነሣንባቸው፣ የተደሰትንባቸውና ያለቀስንባቸው፣ እግዚአብሔርን  ያገኘንባቸው ወይም ከሰይጣን ጋር ማኅበርተኛ የሆንባቸው ሊሆኑ ይችላሉ፡፡  ለዛሬው እንኳን ይህን የምላችሁ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሰፊ ታሪክ ስለተመዘገበለት አንድ ቅዱስ ሰው ልነግራችሁ ፈልጌ ነው፤ ሰውየው ገሊላዊ፣ ትውልዱና ነገዱ ዕብራዊ ሲሆን ያደገው በታላቁ የገሊላ ባሕር አጠገብ ነው ዋና ሥራው አሣ አጥማጅነት ሲሆን የቀደመ ስሙ ስምዖን ወልደ ዮና የክርስትና ስሙ ደግሞ ጴጥሮስ ይባላል፡፡ ይህ ሰው እግዚአብሔር በእርጅና ዘመኑ የባረከው ሰው ነው፤ መቸም እግዚአብሔር ለእያንዳንደችን ያዘጋጃት የመጎብኘት ቀን እንዳለች እናምናለን፣ ከዚህም የተነሣ አንዳንዶችን  በማሕጸን ሳሉ እንደነ ኤርምያስና ዮሐንስ መጥምቅ ያሉትን፣አንዳንዶችን በጨቅላነት እድሜ እንደነ ቅዱስ ቂርቆስ፣ አንዳንዶችን በወጣትነት እንደነ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊና እንደነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያሉትን አንዳንዶችን በእርጅና ዘመናቸው እንደነ ቅዱስ ጴጥሮስ ያሉትን ጎብኝቷቸዋል ፡፡ ከሰው የሚጠበቅ የሚጎበኝበትን ቀን ደጅ መጥናት ነው እንጅ ሌላው የእግዚአብሔር ድርሻ ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም እግዚአብሔር የወሰነለት ቀን ስትደርስ በትጋት ሆኖ ከሚሠራበት ቦታ ሂዶ ጎበኘው፣ ለ...

አትነካኪኝማ

Image
  ተይ አትነካኪኝ አትቀስቅሽኝ እቴዋ ትዝታችን ላይ ነው የተኛሁ የጊዜን ምንጣፍ አንጥፌ አትነካኪኝ ልረፍበት አትቀስቅሽኝ ከእንቅልፌ አትወስዉሽኝ እቴዋ ከነካካሽኝማ በጊወርጊስ በተስኪያን በመንገዱ ዳር አልፌ አደባባዩን ዙሬ በዘንባባው ጥግ ታጥፌ አንድ ጊዜ ካፌው በር ላይ ሌላ ጊዜ መናፍሻው እዚያ ከወፎች መንደር እዚያ ከፍቅር ዋሻው መናፈሻው… አስታውስሺው? ሌላ ጊዜ ከሰፈርሽ ሌላ ጊዜ ከሰፈሬ ከተሰገሰገበት ሚስጥርሽና ሚስጥሬ ሌላ ጊዜ በጸሃዩ ሌላ ጊዜ በምሽቱ መጨለሙን መች አስቤው ልቤ ያለ ከመንጋቱ፡፡ ታስታዉሻልሽ ግን… ከጠዋቷ ጸሃይ ጋር እኩል ነበር ምጠብቅሽ ልቤን ቅልጥ የምትለው አንድም በብርሃኗ አንድም  ደግሞ በፈገግታሽ፡፡ አትነካኪኝ እቴዋ ከነካካሽኝማ ትናንትናን እያሰብኩ ነገየን እየረገጥኩ ህልሜን እየደፈጠጥኩ ተስፋየን እየገደልኩ በሃሳብ ሽምጥ ግልቢያ ትናንት ላይ እደርሳለሁ ያንን ጊዜ አነሳለሁ ድሮአችንን አነግሳለሁ አሁኔን እቀብረዋለሁ በዛሬ ጀምበር ላይ ቆሜ ትዝታሽን እኖራለሁ፡፡ አትወስዉሽኝ አለሜ ዛሬ ላይ ተገትሬ ልጅነታችንን ያሰብኩለት ያ መነፋፈቃችን ያ መፈላለጋችን የመዋደዳችን ግለት በጊዜ ምድጃ ላይ ቀናትን እያነደደ ትዝታ የሚባል ጉቶ እቶኑ ዉስጥ እየማገደ የፍቅርን ፍም እሳት ያፈልቃል ደክሞት የተኛን ገላ፣ የተኛን ልብ ያሞቃል፡፡ አታስታዉሽኝ እቴዋ አታሰሚኝ ድምጽሽን አታሳይኝ ከንፈርሽን አታስታዉሽኝ ፈገግታሽን …ጥርስሽን ያሰብኩለት ተደርድረው በመደዳ ከህሌናየ ላወጣሽ ለራሴ የማልኩትን ቃልን ነው የምከዳ!!! ተይ አትነካኪኝማ ተይ አትወስዉሺኝማ ተይ አትቀስቅሺኝማ ተይ ተይ ተይ                ...

ከላሊበላ ሰማይ ስር Lalibela

Image
አሁን ይህንን ስጽፍልህ 100 ግራም ገለምሶ ይዤ ከተቀመጥኩበት ቦታ ላይ ሊሆን ይችላል፡፡ አንተም ከዚህ የተለየ ነገር እያደረግህ እንዳልሆነ ስነግርህ ያለጥርጥር ነው፡፡ ግድ የለም በርጫ ሙድ ላይ አይደለህም እንበል…ግን የሰፈር አረቄ ቤት ዉስጥ አረቄን በሲጋራና   በአሉባልታ እያወራረድክ ነው፡፡ እሱ ላይ ባትሆንም ደግሞ መንገድ ላይ ድድ እያሰጣህ   አላፊ አግዳሚ ታሸማቅቃለህ…ትለክፋለህ፣ትስቃለህ……መሳቂያ!!! በሌለንበት በሃሜት…   ላልከኝ ወዳጄ ደግሜ እልሃለሁ አትፍራ ከማማት ልቆጠብና ቢሮ ዉስጥ ነህ እንበል ግን ቢሮህ ዉስጥ ብትሆንም ወንበር እያለፋህ የምሳ ሰዓት መድረስን ትጠባበቅ ይሆናል ወይም ደግሞ ልክ እንደ ጀበና ቡና ኮምፒተር ላይ ተጥደሃል   ማለቴ ፌስ ቡክ ላይ፡፡ እና እልሃለሁ ቢሮ ዉስጥ ሆነህ ስራ ካልሰራህ ጫት ቤት ከተቀመጠው … መንገድ ላይ ድድ ከሚያሰጣው በምን ልለይህ…አረቆ ከሚጋተውስ በምን ተሸልክ….በምንም!! ብቻ የትም ሁን የት ብትሰራም ባትሰራም ቅሉ የዚህ ትዉልድ አባል ነህ፡፡ ይቅርታ የስድብ ናዳ አወረድኩኝ ልበል ምን ላድርግ በቆምኩበት ብትቆሙ ያየሁትን ብታዩኮ እንደ እሳት ላንቃ የሚገርፍ የማንነት ስሜት ከዉስጣችሁ ሲገነፍል ታዩት ነበር፡፡ ወዳጄ አሁን በላሊበላ ተራሮች ስር ነኝ፡፡የንጉስ ላሊበላ የእጅ ስራና ጥበብ ካረፈባቸው ድንቅ ዉቅሮች ስር፡፡ ግን ምን ያደርጋል ማመን አቃተኝ፡፡ -የሰው ልጅ እንዴት ከአንድ ድንጋ እነዚን ግዙፍ አቢያተክርስቲያናት ሊሰራ ይችላል….እኛምኮ የሰው ዘሮች ነን አዷማ ይዘን፣በዲጅኖ ታግዘን በመዶሻ ደብድነብ ሜ አንድ ሜትር ድንጋይ ፈለጥንና -እነዚ በድንጋይ ላይ የተጠረቡ ቅርጻቅርጾችና አምሳላት እንዴት እዉን ሊሆኑ ቻሉ -እነዚያ 900 በላይ አመታትን ...

ሳስበው ደከመኝ

Image
ሴትን ልጅ ስትመርጣት አጋር ለህይወትህ ዉስጥ ዉበቷን እንጂ ዉጯ እንዳያስትህ እኔም እንዲሁ ነኝ ዉበት ረጋፊ ነው  ዉስጤን ተመልከተኝ ብለሽኝ ነበረ… ግና….. ከባለጌ ጡትሽ መረን ከለቀቀው ከቀዩ ከንፈርሽ ከተለቀለቀው ከሸምበቆ ባትሽ እንደ ፍም ከቀላው ከፌዘኛ ሳቅሽ አዉሬ ከሚያስበላው ከአሽሙረኛ ዳሌሽ በኩራት ከሰፋው ከሱናሜ ጥቅሻሽ መንገድ ከሚያስጠፋው ፤፤ ፤፤ ዙሪያ ገባሽ ሁሉ ከልሎት የአጋም ሾህ አጥረሽው በአጣና በየት አልፌ ነው ጸባይሽን የማየው  ውስጥሽን ማጠና!? እ….. ሳስበው ደከመኝ!!! Hab. A

የህልሜ ጓደኛ 3

Image
ከክፍል 2 የቀጠለ....  Part 1 link , part 2 link ‹‹ስለአንተ ሁሉን ነገር ነግሬዋለሁ፡፡ ከተዋወቅን ስድስት ወር እንደሆነን… ስንቀሳቀስ ሁሌም የአንተን ባጃጅ እንደምጠቀም… የምፈልገው ቦታ እንደምታደርሰኝና እንደምትመልሰኝ… ከለካፊዎች እንደምትጠብቀኝ… እንደምታዝናናኝ… እንደምታጫዉተኝ… ባጃጅ መንዳት እንደምታለማምደኝ… እና ደግሞ…›› የጀመረችውን ዓረፍተ ነገር ሳትጨርሰው አይኗን እንደጨፈነች ተመስጣ ጥርሷን ብቻ ስታሳየኝ ቆየች፡፡ ከዚያ አይኞቿ ተከፈቱ፡፡ ‹‹…እና ደግሞ… እንደ.ም.ወ.ድ.ህ ጭምር!›› በጠራራ ፀሀይ… ወለል ባለ ብርሀን… የሚርመሰመስ ህዝብና መኪና ባለበት መንገድ ዳር… በዚህ ሁሉ መሀል እኔነቴን ማን ዘረፈኝ? ድምፄንስ ምን ዘጋው? ምክንያቱን ሳላውቀው ድጋሚ ጸጥ አልኩ፡፡ ድርቅ እንደ እንጨት! ከኋላየ መጥታ እጇን ጫን ስታደርግብኝ ባለሁበት ቅዠቴ ጀመረኝ፡፡ የተቀደሰ ቅዠት፡፡ ቅዠቱ እንዲህ ሲል ይጀምራል፡- እኔና ሳሮን ነጭ በነጭ ሙሉ የባህል ልብስ ለብሰን፣ መላዕክቱን መስለን በተቆናጀች ባጃጄ ወደ አባቷ ቤት እንቀርባለን፡፡ አባቷ ነጭ በነጭ የሆነ ሙሉ የባህል ልብስ ለብሰው የቤታቸው ሰገነት ላይ በሩቁ ይታዩናል፡፡ የሆኑ ከየት መጡ ያላልናቸው ሁለት ነጭ መለዮ የለበሱ ሰዎች ሳሮንና እኔን ግራና ቀኝ አጅበው ወደ አባቷ አቀረቡን፡፡ /ያ-ቅዠት የት ሄደ? ያ- የሰይጣኖቹ?/ ሳሮን እሮጣ ሄዳ አባቷን ጥምጥም ብላ ከሳመቻቸው በኋላ ወደኔ እየጠቆመች ‹‹አባየ የነገርኩህ ልጅ ይኼ ነው›› ስትላቸው ከሳሮን በፈጠነ ሮጬ እግራቸው ስር ተደፍቼ ጉልበት ሳምኩ፡፡ ከየት መጣ ያላልኩት ወታደር ከእግራቸው ስር ለአክብሮት የተንበረከክሁትን እኔን በአንድ እጁ አንጠልጥሎ አነሳኝ፡፡ እንደ ሁኔታው እንዳንጠለጠለኝ ሊወረውረኝ ያሰበ ይመስል ነ...

የህልሜ ጓደኛ 2

Image
 (ከክፍል 1 የቀጠለ...) Part 1 link የሳምንቱን ቀናት በሙሉ በስራ ነው የማሳልፈው፡፡ ሰው ሳደርስ ሰው ስመልስ፡፡ ቢሆንም ግን የሰንበት ቀናት አልፈው ሰኞ ሲመጣ እኔም ልክ ሁለት ቀን እረፍት እንደቆየ ሰራተኛ ሁሉ በሞራል እና በወኔ አዲስ ሰው ሁኜ ለስራ እነሳለሁ፡፡ የመንግስት ሰራተኛው ቅዳሜና እሁድን እረፍት አድርጎ ሰኞን በአዲስ መንፈስ ሲቀላቀል እኔ ምንም እረፍት ሳይኖረኝ ሁሌም ልክ እንደ ሰራተኞች በአዲስ መንፈስ ነው የምቀበለው፡፡ ዛሬ ግን ሰኞ አስቀየመኝ፡፡ እንደ ድሮው በአዲስ መንፈስ ልቀበለው ተዘጋጅቼ ወደ ባጃጅ ሽቀላየ ስወጣ እሱ ግን ፊቱን አጨፈገገብኝ፡፡ የስራ መንፈሴን አቆሸሸው፡፡ ፈረንጆች ሰኞን ‹‹ብላክ መንደይ/ጥቁሩ ሰኞ/›› ይሉታል ሲባል ከሰኞ ጋር የቆየ ቂም ይኖራቸው ይሆናል እላለሁ፡፡ ምናልባት ፋሽስት ጣሊያን በሃብሻ አርበኞች ድባቅ የተመታበት ሰኞ ቀን ቢሆንስ? ለዚያ ይሆናል ሰኞን የሚጠሉት፡፡ እኔ ግን እስከ ዛሬዋ ቀን ድረስ ሰኞን ከማክሰኞና ከቅዳሜ ለይቸ አላየውም- ያው እንደ ሌሎች ቀናት ሰኞም ቀን ነው፡፡ ሰኞም ባጃጅ ላይ እሰራለሁ፤ ማክሰኞም፣ ረቡዕም፣ አርብም… ወ.ዘ.ተ እንደተለመደው፡፡ ዛሬ ብቻ ነው ሰኞ ጥቁር የሆነብኝ ‹ብላክ መንደይ›! ጠዋት እንደተለመደው እንጀራ ፍርፍር ሰርቼ ቁርስ አድርጌ ልወጣ ሽንኩርት ከትፌ፣ ዘይት ጨምሬ ልክ በርበሬ ልጨምር ስል መብራት ድርግም አለ፡፡ ምን አለበት በርበሬ እስክጨምር ድረስ እንኳን ቢታገሰኝ? ይኸው የዛሬን ሰኞ ሳልፈልግ ለመፆም አቋም ያዝኩ፡፡ በቀጥታ ወደ ባጃጅ ስራየ በመግባት በመስመር ወረፋ ጠብቄ አራት ያህል ቢያጆ ከመስራቴ ባጃጄ መንገድ ላይ ተንተፋትፋ ቆመች፡፡ እንደ ዛሬ አማርሬ አላውቅም፡፡ በቃ ሰኞን ጠላሁት… black Monday ብቻ ሳይሆን የሆነ ‹...

የህልሜ ጓደኛ 1

Image
ቤታቸው ከአራት ኪሎ ቤተ-መንግስት የሚተናነሰው ጠቅላይ ሚንስተሩ እዚያው ባለመኖራቸው ብቻ ነው፡፡ ልጥጥ ያለች የባለሀብት ልጅ፡፡ ያውም የባለስልጣን፡፡ ግቢያችውን ላስተዋለው አንድን የተከበረ ጫካ በማን አለብኝነት ወርሰውና መሀሉን አስመንጥረው መኖሪያቸውን እዚያ የመሰረቱ ይመስላል፡፡ ከውጭ ሆኖ ለተመለከተው ግቢው የቤተ-ክርስቲያን ቅጽር ወይም የሆነ ፓርክ ይመስላል፡፡ ግቢውን ከከተማው አስፓልት የሚያገናኝ አንድ ጠበብ ያለ የአስፋልት መንገድ አለ፡፡ መንገዱ ከዋናው መስመር ይገነጠልና ከሁለት እሰከ ሶስት የሚሆኑ የሚያማምሩ ቤቶችን ካለፉ በኋላ ቀጥ ባለ አስፋልት ወደነ ሳሮን ቤት ያደርሳል፡፡ አሰፋልቱ ግራና ቀኝ በተተከሉና ቅጠላቸውን በታቀፉ ዛፎች መካካል የተዘጋ ነው፡፡ ማዶና ማዶ ያሉት ዛፎች ወዳጅነት መስርተው በአየር ላይ ቅርንጫፎቻቸውን አስተቃቅፈዋል፡፡ ውስጥ ለውስጥ በአስፋለት መንገዱ አብዛኛውን ጊዜ ሁለት መኪኖች ሽር እያሉ ይወጣሉ ወይም ይገባሉ፡፡ አንደኛው የአባቷ ፕራዶ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በብዛት እሷ የምትነዳው ራቫ ፎር፡፡ ከግቢው አጠገብ ዘበኛው አይጠፋም፡፡ ዘበኛው ማለት የሚከብድ ቢሆንም ያው ዘበኛ ስለሆነ ምንም ሊባል አይችልም፡፡ የሚያምር ጥቁር ጨርቅ ሱሪ ከነጭ ሸሚዝ ጋር ለብሷል፡፡ ካራቫት አላሰረም፤ የላይኞቹ ሁለት የሸሚዙ ቁልፎች አልተቆለፉም፡፡ የሸሚዙ ያለመቆለፍ ከአንገቱ ላይ ላንጠለጠለው የብር ሀብል የተመቸው ይመስል ሀብሉ ደረቱ ላይ ያብረቀርቃል፡፡ ዘበኛነቱን ያወቅሁት እንግዳ ሲመጣ በር ሲከፍትና መኪና ከወጣ በኃላ መልሶ በር ሲቆልፍ ነው፡፡ ልዩ የሆነ ስነ-ምግባር አለው፡፡ የሸሚዙን እጅጌ በሁለት ጊዜ ድግግሞሽ ወደ ላይ ቀንፎታል፡፡ ክንዱ አካባቢ ያለው የእጁ ዉፍረትና የሰፋው ደረቱ ላይ ማራኪ ባህሪው ታክሎበት በወታደራዊ ስነምግባ...

የከሸፈ ትውልድ 3

Image
የመጨረሻው ክፍል Last Part ከዚህ ርዕስ ሳልወጣ አንድ ወርክሾፕ ላይ የታዘብኩትን ገጠመኝ ላካፍልህ፡፡ አወያዩ የሆነ ጠንከር ያለ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ ሲያወያዩን ከቆዩ በኋላ ‹…እስኪ ቤታችሁ ዉስጥ የእናት ሀገራችሁን ሰንደቅ አላማ የሰቀላችሁ ወይም ያስቀመጣችሁ?› ብሎ ጠየቀ፡፡ ከአዳራሽ ሙሉ ተሰብሳቢ መካከል አንድ እንኳን ‹እኔ› ብሎ እጁን ያወጣ አልነበረም፡: (የክፍል 1 ሊንክ) (የክፍል 2 ሊንክ ) ሰዉየው በአግራሞት እየተመለከተን ‹ባንዲራ ቤቱ ያለው የለም?› ሲል ድጋሜ ጠየቀ፡፡ አሁንም ጸጥታ እንጂ ምላሽ አልነበረም፡፡ ሰዉየው ፈገግ ብሎ ንግግሩን ቀጠለ ‹እሽ! የድሮው ባንዲራም ቢሆን?› ሲል ሶስት እድሜ ጠገብ አባቶችና ብዛት ያላቸው ወጣቶች እጃቸውን አወጡ፡፡ ከአጠገቤ የተቀመጠ አንድ ወዳጄ ‹አየህ በሰንደቅአላማችን እንኳን አልተስማማንበትም፤ ይገርማል! የዚች እንቆቅልሽ የሆነች አገር ጉዳይ!› ያለኝን አልረሳዉም፡፡ የሆሊዉድና ቦዉሊድ ፊልም ሰሪዎች ፊልማቸው ዉስጥ አንድም ቀን ስለ እርሻ ስራቸው፣ ስለ አዘራራቸውና ስለ ምርት አሰባሰባቸው አሳይተዉን አያዉቁም፡፡ በተቃራኒው ግን የቡድን ወሲባቸውን፣ ባዕድ አምልኮታቸውንና መረን የለቀቀ ተግባራቸውን ያስኮመኩሙናል፡፡ ዝሙትን፣ ሱስን፣ ስርቆትንና መገዳደልን ይግቱናል፡፡ ተንኮላቸውን እያሰረጹብን እንደሆነ ግን የሚረዳ ትዉልድ የለም፡፡ ግዕዝ ቋንቋችን በጠራራ ፀሃይ ሲዘረፍ ‹‹የዘራፊ ያለሽ ኡ ኡ›› ብሎ ድምጹን ያሰማ አካል የለም፡፡ ከእኛው ምድር በቅሎ ለዘመናት የተመገብነውን ጤፋችንን አይናችን እያየ ‹‹ባለቤት አይደላችሁም፤ ባለቤቶቹ ኔዘርላንዶች ናቸው!›› ስንባል ‹‹ትክክል ናችሁ›› በሚል አይነት እግራችንን አጣጥፈን ተቀምጠናል፡፡ ምን አዚም እንደተደረገብን አላዉቅም፡፡ እነሱኮ የበይ ተመልካቾች አድር...

የከሸፈ ትውልድ 2

Image
ክፍል 2 - Part 2 ከወራት በኋላ የቀን ዉሎ ማስታዎሻየ ላይ የተጻፉ ነገሮችን እያገላበጥኩ ስመለከት የፕሮፌሰሩን ንግግሮች አገኘኋቸው፡፡ ጊዜ መስጠት አልፈለግሁም፤ ወዲያው ስልኬን አዉጥቼ ለፕሮፌሰር ደወልኩላቸው:: (ክፍል 1 ን ለማንበብ ይጫኑ) ከፕሮፌሰር ሙሴ ጋር ከዩኒቨርሲቲው ግቢ ዉስጥ ከሚገኘው የመምህራን መዝናኛ ክበብ ቡና እየጠጣን ብዙ ነገሮችን ተጨዋወትን፡፡ ለዛሬው ብዙ አድማጭ እንጂ ብዙ ተናጋሪ አልነበርኩም፡፡ የዩኒቨርስቲው ግቢ ደስ ይላል፡፡ ከመንገዱ ዳርና ዳር የሚገኙት ዛፎች ቅርንጫፍ ለቅርንጫፍ ተቃቅፈዋል፡፡ በዚያ ላይ ቅዝቃዜው፡፡ ቀጭኑን የአስፋልት መንገድ የግራ ጠርዝ ይዘን ከፕሮፌሰር ጋር ወደ ግቢው መሃል ዘለቅን፡፡ ግቢው አድሮ አዲስ ነው፡፡ ሲያምርና ሲፈካ ነው የሚያድረው፡፡ የተማርኩበት ግቢ … በተለምዶ ጆኮ ስኩል /Joco school/ ተብሎ የሚጠራው ህንጻ … አለፍ ሲል የተፈጥሮ ሳይንስ ቤተ መጽሃፍት … እነዚህ ብቻ ናቸው ባሉበት ያገኘኃቸው፡፡ ያኔ ተማሪዎች እያለን እንደነበረው ከነ ሙሉ ዉበታቸው አሉ፡፡ አዲስ ነገር የተጨመረው ከቤተ መጽሃፍቱ ጎንና ዙሪያውን የተሰሩት የብረት ጠረንጴዛና ወንበሮች ናቸው፡፡ ‹‹… ተመልከት ይሄ ሰነፍ ተማሪዎች እንደ አሸን የሚፈሉበት ዋሻ ነው ›› አሉኝ ፕሮፌሰር፤ ተማሪዎቹ አንድ ለአምስት እየተደራጁ ወደሚወያዩበት ክብ ሰርተው የተደረደሩ ወንበሮች እንድመለከት እየጋበዙኝ፡፡ ቤተ መጽሃፍቱ አካባቢ በሚገኙት አረንጓዴ ዛፎች መካከል ባሉት ክፍት ቦታዎች አለፍ ...